Thursday, July 8, 2010

 ለፈገግታ
በብዙ የዓለም ሀገሮች በተለይም በሃገራችን በኢትዮጵያ ያላውን የኑሮ ሁኔታ ስናስብ በአዕምሮአችን የሚመጣው የብዙኃኑ ሕዝብ ድኅነትና የጥቂት ሃብታሞች ጣራ የነካ የምቾት ኑሮ ነው፡፡ የድኃውና የሃብታሙ ኑሮ ልዩነቱ የሰማይና የምድር ያህል የተራራቀ ነው፡፡ድሃው በእግዚአብሔር ቸርነት የሚኖር እንጂ የሚላስ የሚቀመስ የሌለው ፍጹም ድኃ ነው፡፡ ሃብታሙ ደግሞ የእግዚአብሔር ቸርነት በዝቶለት ገንዘቡን የት ላድርሰው የሚል ቱጃር ነው፡፡ በዚህ መሃል ያለው ደግሞ የድሃና የሃብታም ክልስ ነው፡፡

ያም ሆነ ይህ ድሃውም ሃብታሙም መካከለኛውም እግዚአብሔር በሰጠው ጸጋና በወሰነለት የኑሮ ደረጃ ይኖራል፡፡ ግን ደግሞ ማኅበራዊ ኑሮ አለና በአጋጣሚ ፤በሃዘን ወይ በደስታ አንዱ ሌላውን የመጎብኘትና የኑሮ ሁኔታውን ማየት እድል ያገኝ ይሆናል ፡፡ብዙ ጊዜ ደሃው ወደ ሃብታም ቤት ለጉልበት ሥራ ወይም ሃብታሙ ሰው ለሚፈልገው ጉዳይ እየጠራው ሊሄድ ይችላል፡፡አልፎ አልፎ ደግሞ ምናልባትም ለቅሶ ካለ ለቅሶ ለመድረስ ሃብታም ወደ ድሃው ቤት ሊሔድ ይችል ይሆናል እንጂ የሃብታሙ እግር ወደ ድሃው ቤት ለመሄድ ያጠረ ነው፡፡ጊዜውም ፍላጎቱም የለውም ፡፡ታዲያ አንድ ድሃ የጉልበት ሠራተኛ አዲስ አበባ ወደ ሚገኘው ቦሌ ሠፈር የሃብታሞችን ቤት የግቢ አትክልት ለመኮትኮትና ሣር ለማጨድ እያሰለሰ ይሄዳል፡፡ሥራውን የጀመረ ሰሞን ጥቂቶቹ ሃብታሞቹ ወደ ቤት ገባ ብሎ ሻይ እንዲጠጣ ይጋብዙታል፡፡ እርሱም ደስ እያለው ይገባና እየተናደደ ይወጣል፡፡

ግን አንድ ቀን እንደህ ሊል ሰማሁት፡፡ የእንጀራ ነገር ሆኖብኝ ነው እንጂ አሁንስ እንደ ሃብታም ቤት መሄድ የጠላሁት ነገር የለም፡፡ እኔም ምነው ለምን አልኩት እሱም የሆነውን ነገር በጥያቄና መልስ አስመስሎ ነገረኝ እኔም ተደነኩኝ በማለት ለፈገግታ ያቀረበልን እኛም ስሙን የማናውቀው አንድ ኢትዮጵያዊ ወገናችን ነው፡፡ እኛም ከአስተያየት መቀበያ ሳጥናችን ውስጥ ስላገኘነው የላኩልንን ደንበኛችንን ከልብ እያመሰገንን አንባቢዎቻችን እንዲያነቡት በማለት በብሎጉ ፊት ለፊት ሰሌዳ ላይ ለጥፈነዋልና ያንብቡት፡፡



No comments:

Post a Comment

አስተያየት