Saturday, January 30, 2010

በአስተዳደር ቦርድ አባላት መካከል የነበረው ጠብ ለሕዝብ ይፋ ሆነ !

ለብዙ ወራት በቦርዱ ቢሮ ታምቆ የኖረው የአስተዳደር ቦርድ አባላት ጠብ ፈንድቶ ዛሬ በሕዝብ ስብሰባ መሃል ተገለጠ፡፡ የሂሳብ ሹሙና የሊቀመንበሩ ቡድን ተብሎ ለሁለት የተሠነጠቀውና ቤተክርስቲያኒቱን ከልማት ይልቅ ወደ ውድቀት እየሳባት ያለው ቦርድ በማስተዳደር ብቃቱ ደካማነት በሕዝብ ሲተች መክረሙ ይታወሳል፡፡

Monday, January 25, 2010

ምርጫውን ለማስቆም ጀንበር ጠልቃለች ወይስ ገና ነች

የዕጩ አስተዳደር ቦርድ አባላት ምርጫ ውጤቱ እንደ ተሰማና የዶክተር ግርማ ደጋፊዎች ማሸነፋቸው እንደታወቀ በእነ አቶ ኢዩኤልና በደጋፊዎቻቸው የቦርድ አባላት መካከል ከፍተኛ መደናገጥና አለመረጋጋትን እንደፈጠረ በቅርብ የነበሩ እማኞች ገለጡ፡

Sunday, January 24, 2010

የአስተዳደር ቦርድ ምርጫው ውጤቱ ይፋ ባይሆንም ታወቀ !

ሰሞኑን በአቶ ኢዩኤል ነጋና በዶክተር ግርማ ደጋፊዎች መካከል ሲካሄድ የሰነበተው የምርጫ ውድድርና ፉክክር በዶክተር ግርማ ቲፎዞዎች አሸናፊነት መጠናቀቁን ከአስመራጭ ኮሚቴ አባላት የሾለከው ዜና ያስረዳል፡፡

Thursday, January 14, 2010

የቦርድ ጠበቃ ማሳሰቢያ !

የክስ መጓተትና የይግባኝ ክስ መቀጠል የጠበቆች ፍላጎትና እንጀራቸውም እንደሆነ ይታወቃል፡፡በዚህ መሠረት የዳኛው ያልተጠበቀ ፍርድና ውሳኔ ትክክል ባለመሆኑ እኔንም በጣም አናዶኛል የሚለው የከሳሾች ጠበቃ ውሳኔው የኔንም ሪከርድ የሚያበላሽ ስለሆነ በራሴው ኪሣራ የይግባኝ ክሱን እቀጥላለሁ ብሎ ጉዳዩን ለከፍተኛው ፍርድ ቤት ይግባኝ በማለት ማቅረቡን ሰሞኑን መሰማቱ ይታወቃል፡፡

Sunday, January 10, 2010

የይግባኝ ክሱ የአስተዳደር ቦርዱን አስቆጣ !

ባለፈው ታህሳስ ወር አጋማሽ ላይ በዋለው ችሎት ሌሎች የክስ ዝርዝሮችን ሳያዩ ዳኛው የሰጡት ብይን ያለግባብባና ፍትህነት የጎደለው መሆኑን የሚገልጹት ከሳሾች ሶስት ዳኞች በሚሰየሙበት ከፍተኛ ችሎት ላይ ጉዳያቸው እንደገና እንዲታይላቸው ይግባኝ ማለታቸውን ለማወቅ ተችሏል፡፡