Wednesday, April 28, 2010

<ልጆቹዋን ከቅጽሯ የሚያባርሩ ጨካኞች ያሏት ቤተ ክርስቲያን ሊለቀስላት ይገባል።›

የአስተዳደር ቦርድ መልአከ ሣህል አወቀን ከሥራ ካሰናበተበት ሰዓትና ደቂቃ ጀምሮ ባደረበት የፍርሃት መንፈስ ባልተለመደ ሁኔታና ከወትሮው በተለየ መልኩ በርካታ የፖሊስ ሠራዊትን ከሌሊቱ 3 ጀምሮ በቤተክርስቲያኒቱ ግቢ ውስጥ እንዲሠማሩ ማድረጉ ብዙውን አማኝ ክርስቲያን አሳዝኗል፡፡

Saturday, April 24, 2010

አምባ ገነኑ ቦርድ መልአከ ሣህል አወቀን ከሥራ አሰናበተ !

ትናንት ቅዳሜ ማምሻውን ለስብሰባ ይፈለጋሉ ተብለው በስልክ ተጠርተው ቦርድ ጽ/ቤት ተጠርተው የቀረቡት መልአከ ሣህል በሚያስተምሩት እውነተኛ የወንጌል ትምህርት ምክንያት እንደ ክርስቶስ በሐሰት ተወንጅለው አስተዳደርን በማያውቅ አምባገነን ቦርድ የስንብት ደብዳቤ ተነቦላቸው ሁለተኛ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እንዳይደርሱ በሴት ፖሊስ ተገደው በመፈረም የስንብት ደብዳቤውን ተረክበው መውጣታቸውን ለማውቅ ተችሏል፡፡

Monday, April 19, 2010

የሂሳብ መርማሪና አጣሪ ኮሚቴ የሥራውን ውጤት አቀረበ !

ሰላም ተዋህዶ ቅዳሜ April 17 2010 በተደረገው ጠቅላላ የአባላት ስብሰባ ላይ ያልተካፈለች ብትሆንም ስብሰባውን የተካፈሉ አንዳንድ ሰዎችን በማነጋገር ያገኘችውን ዘገባ በአጭሩ እንደሚከተለው ዘግባዋለች፡፡

Tuesday, April 13, 2010

ቦርድና ወታደራዊ መግለጫው !

የውብ እንጀራ ኩባንያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፤
በሰሜን አሜሪካ የቴክሳስና አካባቢዋ የኢህአፓ አባላት ሰብሳቢ
የደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ቦርድ ዋና ጸሐፊ ወዘተ… አቶ አበበ ጤፉ ወታደራዊ መግጫ ሰጡ፡፡

Thursday, April 8, 2010

የአስተዳደር ቦርዱ ለአዲስ በቀል እየተዘጋጀ ነው፡፡

ባለፈው ቅዳሜ ምሽት የትንሳኤ ዋዜማ በተአምረ ማርያም መቅድም ንባባ ምክንያት መምሬ ሞገስ ከቤተ መቅደሱ በኃይለኛ የቁጣ መንፈስ ተሞልተው በመውጣት‹ በሕግ አምላክ ፤ በሕግ አምላክ ፤ ሃይማኖት ነው … › እያሉ እንደ አበደ ሰው ደጋግመው በመጮኸቸው ምክንያት ሕዝበ ክርስቲያኑንና የበዓሉን ታዳሚዎች በሙሉ ማስደንገጣቸውና ማሳዘናቸው ይታወቃል፡፡ በአንጻሩም ደግሞ መልአከ ሣህል አወቀ ትዕግሥት በሞላበትና በተረጋጋ መንፈስ ያደረጉት የማረጋጊያ ንግግርና ሲመሩት የነበረው መንፈሳዊ የማሕሌት አገልግሎት ምንም ነገር እንዳልተፈጠረ በማማስመሰል ሊበላሽ የነበረውን በዓል በቦታው እንዲመለስ አድርገውታል፡፡