Wednesday, July 7, 2010

ለምኑ ይሰጣችኋል !
                                       ማቴ 7፡7

እግዚአብሔርን ፈልጎ ያላገኘው ፤ ለምኖም ከእርሱ ያልተቀበለ ሰው የለም ፡፡ ቢሮር እርሱ በእግዚአብሔር ያልታመነ ወይም ለጸሎት የሰነፈ ብቻ ነው፡፡ የተራበ ፤የተጠማ ፤ የታረዘ፤ የተራቆተ፤ በችግር የተጎዳና የመሰከነ ሁሉ ቢለምን እግዚአብሔር ሊሰጠው የታመነ አምላክ ነው፡፡

ምክንያቱም እግዚአብሔር በቅዱስ ቃሉ ‹ ለምኑ ይሰጣችኋል ፤ ፈልጉ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያውን አንኳኩ ይከፈትላችኋል ፡፡ የሚለምን ሁሉ ይቀበላልና ፡፡የሚፈልገውንም ያገኛል፡፡መዝጊያውንም ለሚያንኳኳ ሁሉ ይከፈትለታል፡፡ › በማለት ተናግሯልና፡፡ ማቴ 7 ፡ 7

ከዚህ አንጻር የልመናው ( የጸሎት ) ዘዴው የገባቸው ብልጦች ክርስቲያኖች እግዚአብሔርን በመለመን ብዙ አግኝተዋል፡፡ ስለተደረገላቸው ሁሉ ብዙ አመስግነዋል፡፡ያመሰግናሉም፡፡ ስለዚህ ስለጸሎትና ምስጋና ሰላም ተዋሕዶ ከበራሪ ኢ-ሜይል ያገኘቻትን አጭር የእንግሊዘኛ ጽሑፍ ለአንባቢያን ጠቃሚ ሆኖ ስላገኘችው እንደሚከተለው ታቀርበዋለች፡፡


1 comment:

  1. I got it very worthy for our Christian life.
    You, Blogers, pls go ahead. It is so nice.
    I thank you for the message.

    ReplyDelete

አስተያየት