Tuesday, May 25, 2010

መንፈሳዊ ጉባዔ

ቤተ ክርስቲያን በውጪው ዓለም ስላላት ይዘት

በቤተ ክርስቲያን አገልግሎት የማኅበረ ቅዱሳን ተሳትፎ

ስለ ቤተ ክርስቲያን አንድነትና ሰላም ትምህርት የሚሠጥበትና ውይይት የሚደረግበት 
መንፈሳዊ ጉባዔ

ግንቦት 23 2002 ( May 31 2010)

ከ 5:00 pm ጀምሮ
ቦታ
Crown Plaza on the NW corner of 1635 &  coit Rd.7800 Alfa Rd
Dallas , TX, 75240

 የማኅበረ ቅዱሳንን አገልግሎት በዐውደ ርእይ ይመልከቱ 
 

Saturday, May 22, 2010

Be Aware of a Silent Dog ከዝምተኛ ውሻ ተጠበቁ!

ከላይ በርእስ ለተቀመጠው ኃይለ ቃል ባለቤቱ ቅዱስ ጳውሎስ ነው፡፡ፊል 3፡2፡፡ ይሁን እንጂ እንግሊዞችም Be aware of a silent Dog and still water ከዝምተኛና ከረጋ ውሃ ተጠበቁ ! በማለት ወደ ወግ ቀይረውታል ፡፡ 

Tuesday, May 18, 2010

የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ውዝግብ በቻናል 4 FoX ቴሌቪዥን በአየር ላይ ዋለ



በዚህ ባለንበት በ21ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በዲሞክራሲያዊት ሀገር በአሜሪካ ይህ መደረጉ የሚያስገርም ነው !

Monday, May 17, 2010

ሠበር ዜና

ሚያዚያ 24 2002 ( May 2 2010 ) በዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን የአስተዳደር ቦርድ ቁጥራቸው ከ20 በላይ የሚሆኑ ወንጀለኛን በውሻ የሚፈልጉና ቦንብ ፈታሽ የሆኑ ልዩ የፖሊስ ሠራዊትን ቀጥሮ በቤተ መቅደስ ውስጥ የፈጸመውን ግፍና ድብደባ በተመለከተ በዩቱብ ለአለም የተሠራጨው የቪዲዮ ፊልም የሜዲያን ትኩረትን ስለሳበ ዛሬ ሰኞ May 17 2010 ከምሽቱ 9.00pm ላይ በቻናል 4 ላይ በቴሌ ቪዥን ይተላለፋል፡፡

Sunday, May 16, 2010

የሞኝ ዘፈን ሁልጊዜ አበባዬ ሆይ ነው !

ከላይ ለዚህ ጽሑፍ ርእስ የሆነውን ዓረፍተ ነገር ‹የሞኝ ለቅሶ መልሶ መላልሶ› ነው፡፡ የሚለው የአገራችን ይትበሀልና ተረት የበለጠ ይገልጸዋል፡፡ ሰንበቴ የሚባለው የቦርድ ልሳን የሆነው ብሎግ ከጀመረበት ቀን አንስቶ እንደ ሞኝ ዘፈን ወይም ለቅሶ መላልሶ የሚያሰማው አንድ ነገር አለው፡፡ ይህ ደግሞ ቦርድን በምን መንፈስ እንደሚያስብና እንደሚሠራ ለማን ሲል ደግሞ መከራውን እንደሚያይ በግልጽ መረዳት የሚያስችልና የሚጠቁም ነው፡፡

Friday, May 14, 2010

የሰሞኑ ዜና

የአስተዳደር ቦርዱ መልአከ ሣህል አወቀን ከሥራ ካሰናበተበትና ቀሲስ መስፍንም የአስተዳደሩን የተባላሸ አሠራር በመጠየፍ ሥራቸውን በፈቃዳቸው ከለቀቁበት ቀን ጀምሮ በአስተዳደሩም ሆነ በአባትና ልጅ ካህናት እንዲሁም በምእመናኑ መካከል ውጥረትና አለመረጋጋት መፈጠሩን ታዛቢዎች ይናገራሉ፡፡ ካህናትንና ምእመናንን በማባረር ሰላም አመጣለሁ በማለት ሌት ከቀን ለጥፋት የሚደክመው ቦርድ በስሜትና ባለማስተዋል የፈጸማቸው ከፍተኛ ስህተቶች ከአስተዳደሩ አልፎ በቤተ ክርስቲያኒቱ የወደፊት አገልግሎት ላይ ከባድና አስቸጋሪ ክስተቶች ሊያጋጥሙ እንደሚችሉ አንዳንድ ሁኔታዎች ይጠቁማሉ፡፡

Tuesday, May 4, 2010

እጅግ አስቸኳይ የስብሰባ ጥሪ

እጅግ አስቸኳይ የስብሰባ ጥሪ

በዳላስ የሚገኘውን የቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ከድሮው ጀምሮ በልማት እድገቱ እዚህ እስኪደርስ ድረስ በጉልበታችሁ የደከማችሁና በገንዘባችሁ የተራዳችሁ፤
አሁን ግን በአምባ ገነኑ ቦርድ አባላት አይደላችሁም ተብላችሁ የተሠረዛችሁ የቤተ ክርስቲያኑ መሥራች አባላት በሙሉ

የቤተ ክርስቲያኑ አስተዳደር ከጊዜ ወደ ጊዜ እየከፋና የክርስትናውን መንገድ እየለቀቀ በመምጣቱ ምክንያት እንዲሁም የተረገጠውን የአባላት ክርስቲያናዊ መብት በሕግ ለማስከበር ፍርድ ቤት በመቆም ፍትህን እየጠበቃችሁ ያላችሁ ወገኖች በሙሉ

ክህነታችሁ እውነተኛውን አምላክ ክርስቶስንና ሕዝቡን የሚያገለግል እንጂ በውሸት፤በክህደትና በዛገ ፖለቲካዊ አስተሳሰብ የተበላሸ የቦርድን አሠራር የሚደግፍ ሆኖ ባለመገኘቱ ምክንያት በግፍና በሐዘን ከአገልግሎት የታገዳችሁና የተለያችሁ ክቡራን አባቶቻችን ካህናት በሙሉ

ስለ ቤተ መቅደሱና ስለ አባቶች ካህናት ክብር ስትሉ ሰብአዊነት የሌለው አምባገነኑ ቦርድ በቀጠራቸው ፖሊሶች በቤተ መቅደስ ውስጥ የተደበደባችሁና ያለጥፋታችሁ በእጅ ብረት በመታሠር የግፍን ጽዋን የቀመሳችሁ በሙሉhttp://www.youtube.com/watch?v=QTV8QUwlwFI

የተወሰኑ የቦርድ አባላእራሳቸውን በቡድን በማደራጀት የቤተክርስቲያኒቱን ገንዘብና ንብረትያላግባብ በማባከንና እንዲሁም በጥላቻና በበቀል ላይ ተመርኩዘው የሚሠሩትን ኢክርስቲያናዊ ሥራ በመቃወም እራሳችሁን ከቦርድ አባልነት ያገለላችሁና የቀድሞ የአስተዳደር ቦርድ አባላት የነበራችሁ በሙሉ፤

አረመኔው ቦርድ በሚፈጽመውና በመፈጸም ላይ በሚገኘው ግፍ ምክንያት ማታና ጧት በማዘን የምታለቅሱ የአጥቢያው ቤተክርስቲያን አማኞች አባቶችና እናቶች፤ወንድሞችና እህቶች በሙሉ

በአምባገነኑ አስተዳደና የአስተዳደሩን ክፉ ተግባር በተቃወሙ የቤተክርስቲያኒቱ አባላት መካከል የተከሠተውን ግጭትና የክስ ሂደት በሰላም ፤ በእርቅና በይቅርታ እንዲፈታ ሌት ተቀን የደማችሁ የሠላም ልዑካንና የደብራችን ሽማግሌዎች በሙሉ፤

የደብሩን ሰላምና ፍቅር ወደ ቀድሞ ሥፍራው ለመመለስና በቤተ ክርስቲያኒቱ ላይ ዱብዳ ሆነው የወደቁትን ካባድ ችግሮች በጋራ ለማስወገድ እንዲቻል የፊታችን ቅዳሜ May 8 2010 ቀን 4.00 PM ላይ ታላቅ ሕዝባዊ ስብሰባ ተዘጋጅቷል ፡፡ ስለዚህ ሁላችንም ቀደም ሲል የነበሩ ልዩነቶቻችን ወደ ጎን በመተው ቤተ ክርስቲያኒቱን ከጉልበተኞችና ከአንባገነኖች ለማዳን በሚደረገው በዚህ ስብሰባ ላይ በመገኘት ክርስቲያናዊ ግዴታችንን በጋራ እንድንወጣ በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን፡፡

የሠላም አምላክ ስብሰባችንን ይባርክ !

የስብሰባው ጊዚያዊ አስተባባሪ ኮሚቴ

የስብሰባው ቦታ

Double Tree Hotel Dallas / Richardson
1981 North Central Expressway , Richardson
TX ,75080
972 808 5386