Friday, October 15, 2010



የልጄ ተንኮል ቢያናድደኝም መልሶ ደግሞ አሳቀኝ !
ልጆች የእግዚአብሔር ስጦታዎች ናቸው ሲል ነቢዩ ዳዊት ተናግሯል፡፡ መዝ ፡፡የሰው ልጆችም ይህንን አምላካዊ ቃል ትርጉሙን በትክክል የሚረዱት ባልና ሚስት ሆነው በሚኖሩበት ቤታቸው ውሰጥ ከአብራካቸው የወጣ ህጻን ልጅ ሲያገኙ ነው፡፡ በምጥና በጋር ልጇን ለመወለድ የቀረበች ነፈሰ ጡር ሴት ልጇን በወለደች ጊዜ ምጥና ጋሯን በመርሳት በደስታ ትዋጣለች፡፡ አባትም እንደዚሁ፡፡
የተወለዱ ልጆች ከእንጭጭነት አልፈው ሲፋፉና ድክ ድክ እያሉ ሲወድቁ ሲነሱ ማየት ትልቅ የኅሊና ደስታን ይሰጣል፡፡ ይሁን እንጂ ልጆች በሁለትና በሶስት ዐመት እድሜ ላይ ሲደርሱ በአእምሮ፤ በአካልና በቋንቋ እድገት ቢያሳዩም ለጫወታ እያሉ የሚሠሯቸው አንዳንድ ሥራዎቻቸው የሚያስገረሙና የሚያስቁ ናቸው፡፡ በዚህ እድሜ ደግሞ የወላጆች ጥብቅ ክትትልም እጅጉን ያስፈልጋል፡፡ ልጆች በተለይ ዘወትር ከሚጫወቱበት የቤት ውስጥ ሥፍራ ሰወር ሲሉና ድምጻቸው ሲጠፋ በመጠራጠር የት እንዳሉና ምን እየሠሩ እንደሆነ በቅርብ መከታተል ተገቢ ነው፡፡ ዛሬ ለዚህ ጽሑፍ ምክንያት የሆነን < Family Fun > በመባል በእንግሊዘኛ እየታተመ በሚወጣው የቤተሰብ መጽሔት ላይ ያገኘው የአንድ ቤተ ሰብ ገጠመኝ ነው፡፡ ድርጊቱ እንዲህ ነው፡፡

Thursday, October 7, 2010

እጅግ አደገኛ ነው !
እለቱ እሁድ ነው፡፡ችግሩም የተከሰተው በሰሜን ቴክሳስ ግዛት ውስጥ በቅርብ ቀን ነው፡፡ ሴትየዋ በሚዝናኑበት የጀልባ ፍሪጅ ውስጥ ካስቀመጡት በቆርቆሮ የታሸጉ የለስላሳ መጠጦች መካከል ኮካ ኮላን መርጠው ይጠጣሉ ፡፡በማግስቱ ሰኞ በድንገተኛ አምቡላንስ ተወስደው ወደ ሆስፒታል ይገባሉ፡፡በጣም በመድከማቸው ወደ አይሲዩ( Intensive care unit) ይወሰዳሉ፡፡ብዙም ሳይቆዩ ከሁለት ቀናት በኋላ ረቡዕ ዕለት ሕይወታቸው ያልፋል፡፡ ሀኪሞች ለሴትየዋ ሞት ምክንያት የሆነው ‹ሌፕቶስፒሮሲሰ› በመባል የሚታወቀው አደገኛ በሽታ መሆኑን በምርመራ ያረጋግጣሉ፡፡የዚህ በሽታ ምልክት ደግሞ ሴትየዋ ከጠጡት የኮካኮላ ቆርቆሮ መጠጫ ቀዳዳ አካባቢ ባለው የቆርቆሮው አካል ላይ በምርመራው ይገኛል፡፡
የአይጥ ሽንት መርዛማና ሰው ሊገድል የሚችል አደገኛ ‹ሌፕቶስፒሮሲሰ› መርዝ በውስጡ እንደለው የሳንይስ ምርምር ውጤት ያረጋግጣል፡፡በዚህ መሠረት ሴትየዋም የሞቱት በለስላሳ መጠጥ ማመርረቻም ሆነ በማከፋፈያ ትላልቅ መጋዘኖችና በየመሸጫ መደብሮች ውስጥ የሚኖሩ አይጦች በላዩ ላይ በመሄድና በላዩ ላይ በመሽናት የተበከለውን የኮካኮላ ቆርቆሮ ሳያጥቡ ከነመርዙ አፋቸው ላይ ደቅነው በመጠጣታቸው ምክንያት ነው፡፡