Tuesday, September 21, 2010

የአህዮች እናት እንደምን አደሩ?

በአንድ የገጠር መንደር ውስጥ ሁለት አህዮች ያሏቸው አንድ አሮጊት ሴት ነበሩ፡፡በዚያው መንደር ውስጥ ደግሞ አሮጊቷ ሴት አህዮቻቸውን እየነዱ ዘወትር በሚመላለሱበት መስቀለኛ መንገድ ላይ የተከመረ ድንጋይ ነበር፡፡ በዚያ ላይ ተኮልኩለው አላፊ አግዳሚውን የሚተቹና የሚተርቡ ስነ ምግባር የጎደላቸው ጥቂት ወጣቶች ነበሩ፡፡ እነዚህ የመንደር ጎረምሶች እንደ ለማዳቸው አሮቷ ሴት አህዮቻቸውን በጧት እየነዱ በዚያ መንገድ ሲያልፉ አሮጊቷን ለማብሸቅ ብለው ‹ የአህዮች እናት እንደምን አደሩ ? › አሏቸው ፡፡ ሰላምታው የተረብ መሆኑ የገባቸው አሮጊቷም መለስ አድርገው ‹ እግዚአብሔር ይመስገን ልጆቼ ! እንደምን አደራችሁ ፡፡ › ብለው አጸፋቸውን መለሱ፡፡

No comments:

Post a Comment

አስተያየት