Thursday, September 9, 2010

ለምን የሚጠቅመንን አንለምንም ?
አንድ እራሱን በጣም አድረጎ የሚወድ ሰው ሁል ጊዜ ‹ እግዚአብሔር ሆይ ስጠኝ ስጠኝ ስጠኝ ... › እያለ አዘውትሮ ይጸልይ ነበር ፡፡ የነገሩትን የማይረሣ የለመኑትንም የማይነሣ አምላክም አንድ ቀን ተገለጠለትና ‹ ጸሎትህን ሰምቼ አሁን የምትሻውን ነገር ሁሉ ላደርግልህ መጥቼአለሁና ደስ ይበልህ ! አለው፡፡ ሰውየውም ጸሎቱን ሰምቶለት እግዚአብሔር ወደ እርሱ ስለመጣ እጅግ በጣም ደስ አለው፡፡እግዚአብሔርም መልሶ ‹አንተ የለመንከኝን ነገር ሁሉ እጥፍ አድርጌ ለጓደኛህም እሰጠዋለሁና ምን እንዳደርግልህ ትፍጋለህ ? አለው፡፡ ይህን ጊዜ ሰውየው ባዘነ መንፈስ ትንሽ አሰብ አደረገና ‹ ጌታ ሆይ እንግዲያውስ አንድ አይኔን አጥፋው ፡፡ › ብሎ አረፈ ፡፡ የእርሱ አንድ ዓይን ሲጠፋ የጓደኛ ሁለት ዓይኑ ይጠፋልና፡፡

1 comment:

  1. please don`t write the name of God in jokes.
    Jesus is the Son of God I think we are familiar with this name in our understanding that is why we call this name unnecessarily. When we said Jesus is the son of God it is not as what we know we are from our parent He is equal to God. my second opinion is since christian means the follower of Jesus where you get from cursing people on internet? I think you have to read history about Mariam Megdelawit , Simon, feyetawi Zeyeman , and so .... on I t think before we giving an advice for some one else we have to change our self to the real christian otherwise we are joking in our Life. do you think Jesus support you for cursing people He dying for. if you accept this advice i am ready too.

    ReplyDelete

አስተያየት