Tuesday, June 1, 2010

ማኅበረ ቅዱሳን ጉባዔውን በመልካም ሁኔታ ጀምሮ አጠናቀቀ !

በሰሜን አሜሪካ የሚገኘው የማኅበረ ቅዱሳን 12ኛ መደበኛ ጉባዔ በዳላስ ከተማ ተካሄደ ፡፡
ከ May 28 - 30 ድረስ በቆየው በዚሁ ጉባዔ የዓመቱ የማኅበሩ ሥራዎች ግምገማ ሪፖረት የቀረበ ሲሆን የቀጣዩን ዓመት የሥራ ዕቅድና በጀትንም አጽድቋል፡፡http://www.timeanddate.com/worldclock/fullscreen.html?n=7
;

አስካሁን ከተደረጉት የማኅበሩ ዓመታዊ ጉድባዔያት በዐይነቱና በይዘቱ ከፍተኛ ነው በተባለው በዚሁ ጉባዔ የሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ ኤዎስታጤዎስ የተገኙ ሲሆን ከተለያዩ የአሜሪካን ግዛቶች በርከት ያሉ ካህናትና ከመቶ ሃያ በላይ የሚሆኑ የማኅበሩ አባላት በተወካይነት ተካፋይ ሆነዋል ተብሏል፡፡
ይህንኑ የሰሜን አሜሪካ 12ኛውን ዓመታዊ በዓል ምክንያት በማድረግ May 31 2010 በክራውን ፕላዛ ሆቴል ውስጥ በተዘጋጀው ትምህርታዊ ጉባዔ ቁጥሩ ከ 200 በላይ የሚሆን ህዝብ የተገኛ ሲሆን ስለ ማኅበረ ቅዱሳን አመሠራረትና ማኅበሩ በቤተክርስቲያን ውስጥ ስላለው ተሳትፎ ከማኅበሩ ምሥረታ ጀምሮ በነበሩና ማኅበሩን በከፍተኛ ሁኔታ እያገለገሉ ባሉ አባቶችና ወንድሞች ሰፊ ገለጻና ትምህርት ተሰጥቷል፡፡ በዚሁ ትምህርታዊ ጉባዔ መልአከ ሳሌም አባ ገብረ ኪዳን ፤ መልአከ ሰላም ቀሲስ ያሬድ ገብረ መድኅንና ዲያቆን ኤፍሬም እሸቴ በተጋባዥ መምህርነት ተሳትፈዋል፡፡
በዚሁ ጉባኤ ማህበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያም ሆነ በውጭው አለም ለቤተክርስቲያኒቱ ያበረከተውንና እያበረከተ ያለው የሙያ፤የገንዘብ፤የጉልበትና የስብከተ ወንጌል አገልግሎት በእውነተኛዪቱ የቤተ ክርስቲያን ልጆች ሁሉ እንዲወደድና እንዲደገፍ ያደረገው ቢሆንም የቤተክርስቲያናችን መሠረታዊ ጠላቶች የሆኑ መናፍቃንና አስመሳይ ፖለቲከኞች ግን የስም ማጥፋት ሥራዎችን እንደተያያዙትም ተገልጧል፡፡ ይሁን እንጂ ሕዝቡም ለመናፍቃንና ለእነዚህ አስመሳይ ፖለቲከኞች ፕሮፓጋንዳና የሐሰት ወሬ ጆሮውን እንደማይሠጥና ዳግመኛ እንደማይወናበድ ውስጣዊ ስሜቱን በቁጭትና በቃላት ገልጧል፡፡

በመጨረሻም ሕዝቡ ስለቤተክርስቲያን አጠቃላይ ገጽታዎች ግንዛቤንና እውቀትን እንዲያገኝ እንዲህ ዓይነት ጉባዔያት በተወሰኑ ወራት ሊዘጋጁ እንደሚገባ በማሳሰብ የጉባዔው ፍጻሜ ሆኗል፡፡






2 comments:

  1. Our Ethiopian Orthodox Church must be lead by the church leaders who knows about the "Fitha-Negest", "Degua", "Bible" from A-Z ec. not by the bunch of thives. First of all the present board members must be step down. The present church policy, procedure and regulations must me approved by the whole members of our church. The board members election must be offical not secret. Aba Moges and his son prist Yohanes must be suspended and we need Orthodex educated leader of the church (Yedeber Aleka). He is the one who must lead the board members.
    Thanks,
    May God give us peace for our church!!
    June 2, 2010 10:44 PM

    ReplyDelete
  2. Thank you Selam-Tewahedo for the wonderful news article you posted here.

    ReplyDelete

አስተያየት