Saturday, May 22, 2010

Be Aware of a Silent Dog ከዝምተኛ ውሻ ተጠበቁ!

ከላይ በርእስ ለተቀመጠው ኃይለ ቃል ባለቤቱ ቅዱስ ጳውሎስ ነው፡፡ፊል 3፡2፡፡ ይሁን እንጂ እንግሊዞችም Be aware of a silent Dog and still water ከዝምተኛና ከረጋ ውሃ ተጠበቁ ! በማለት ወደ ወግ ቀይረውታል ፡፡ 

ባለንበት ሀገር በአሜሪካና በሌሎች በሥልጣኔ ባደጉ ሀገሮች የሚኖሩ ውሾች በአፍሪካና በቤሎች ባላደጉ ሃገሮች ከሚኖሩ ወሾች የተለየ ባሕርዪ እንዳላቸው ግልጽ ነው፡፡

በሃገራችን ያሉ ውሾች ከልጅነታቸው ጀምሮ የሚታሠሩና በጨለማ ቤት ተዘግቶባቸው የሚውሉ ከሆነ በባሕሪያቸው ኃይለኞችና ተናካሾች ይሆናሉ፡፡ አንዳንድ ውሾች ደግሞ ስለማይታሠሩና ከሰዎች ጋር በመንደር ስለሚውሉ የኃይለኝነትና የተናካሽነት ጠባይ ላይታባቸው ይችላል፡፡ እየተቅለሰለሱና ጅራታቸውን እያወዛወዙ ጠባያቸውን አሳምረው ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ለመኖር ይሞክራሉ፡፡ ታዲያ እንዲህ ዓይነት ውሾች በመንደሩ ሰዎች ዝምተኞች ውሾች በመባል ይታወቃሉ፡፡ይሁን እንጂ በተፈጥሮአቸው ያው ውሾች ናቸውና ዝምተኞችና ሰላማውያን መስለው ቢታዩም አዘናግተው የሰው እግር የሚዘነጥሉበት ጊዜ ስለሚኖር እንግሊዞች ‹ከዝምተኛ ውሻ ተጠበቁ!› በማለት ይተርታሉ፡፡

የዚህ ጽሑፍ ዓላማ የውሾችን ባህርዪና ጠባይ ለማተት ሳይሆን በተፈጥሮአዊ ባሕርዪው ዝመተኛ ውሻን የሚመስል አንድ ሰው ስላገኘን እሱን ለማስተዋወቅ ነው፡፡ አካል ጉዳተኛ በመሆኑ የማያውቀውና ድንገት የሚያየው ሰው ሁሉ በኃዘን ከንፈሩን የማይመጥለትና ‹ሲያሳዝን› የማይለው የለም፡፡ስሙ አገሬ ይባላል፡፡ የትውልድ አገሩ ሐረር አካባቢ ነው፡፡ በተፈጥሮ ባጋጠመው የአካለ ስንኩልነት አደጋ ምክንያት አንኛው እግሩ ከአገልግሎት ውጪ ስለሆነ የባለአራት እግር የአካል ጉዳተኞች ተሸከርካሪ ተጠቃሚ ነው፡፡አንዳንዴም የምርኩዝ እንጨትን ለድጋፍ ይጠቀማል፡፡ከመወለዱ ጆምሮ ባጋጠመው የአካል ጉዳት ምክንያት የትምህርትና የምግብ እርዳታ ለማግኘት ኩየራ በሚገኘው የፕሮቴስታንት ሚሽነሪ አዳሪ ት/ቤት በመግባት እዚያው እየተረዳ ያደገ ነው፡፡ ከዚህ አንጻር ሃይማኖቱም ኦርቶዶክስ ሳይሆን ከልጅነቱ ጀምሮ ያደገበት ሃይማኖት ፕሮቴስታንት ነው፡፡ 

አቶ ሃገሬ ወደ አሜሪካን ሃገር ከመጣበት ጊዜ ጀመሮ በኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንና በፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አባል በመሆን ሁለቱምጋ በአንድ ሳምንት ልዩነት በየተራ በመገኘት ስውር ሥራ የሚሠራ አደገኛ ሰው ነው፡፡ 

አቶ ሃገሬ በኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በአስተዳደርም ሆነ በምእመናን መካከል የሚፈጠረውን የአለመግባባት ክፍተት በመጠቀምና ይህንኑ በፈጠራ ወሬና በአሉባልታ በማስፋት እንዲሁም ሰዎችን በማጣላትና በማለያየት ሰዎች የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን እንዲጠሉና ትኩረትና የወደፊት አቅጣጫቸው ወደ ፕሮቴስታንቱ ሃይማኖት እንዲሆን መንገዶችን የሚጠቁምና ሁኔታዎችን የሚያመቻች ምንደኛ ሰው ነው፡፡ ለዚህም በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ጭቅጭቅ እንደሰለቸውና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ የሚያየውና የሚሰማው ነገር ሁሉ ወደ ፕሮቴስታንት ሃይማኖት እንዲሄድ እንደሚገፋው እያስመሰለ እዚያ ብንሄድ ይሻላል እያለ ብዙዎችን ከቤተ ክርስቲያን የሚያስወጣ ነጣቂ ተኩላ ነው፡፡ ለዚህ ሥራውም ከፕሮቴስታንት ቤተ ክርስቲያን ድርጎን እየተቀበለ ያለ ሰው ነው፡፡

አቶ ሃገሬ ያካበተውን ከፍተኛ የኮምፒውተርና የግራፊክስ እውቀት በመጠቀም ፎርጅድ ዶክመንቶችን የሚሠራ ነው፡፡

አቶ ሃገሬ በተለያዩ ጊዜያት የተነሱ የማይገናኙ የፎቶ ምስሎችን ቀዳዶ በማገጣጠምና አንድ ላይ በማገናኘት ሰዎችን ለመወንጀልና ችግር ውስጥ ለመክተት ፎርጅድ ፎቶዎችን የሚሠራ ተንኮለኛ ሰው ነው፡፡

አቶ ሃገሬ በተለያዩ ጊዜያት የተቀረጹ የቪዲዮ ካሴቶችን በኤዲቲን ቆርጦ በመቀጠል የማይገናኙና በጭራሽ የማይተዋወቁ ሰዎችን አብረው በጎ እደሠሩ ወይም እዳጠፉ አድርጎ በፎርጅድ ሠርቶ በማሰመሰል የሚያወጣ አደገኛ ሰው ነው፡፡

አቶ ሃገሬ በተለያዩ ጊዜያት በድምጽ የተቀረጹ ትምህርቶችንና ንግግሮችን ቆርጦ በማውጣትና በሌላ ጊዜ ከተሠጡ ትምህርቶች ወይም በሌላ ጊዜ ከተነገሩ ንግገሮች ጋር በማገናኘት ለመጥፎ ሠራ የሚውል ፎርጅድ የድምጽ ካሴትን ሠርቶ የሚያቀርብ ሠይጣናዊ መንፈስ ያለው ሰው ነው፡፡
አቶ ሃገሬ በእነዚህ ሁሉ ሥራዎቹ በቨርጂኒያና በአካባቢዋ ነዋሪ ኢትዮጵያውያን ዘንድ በዚሁ የተንኮልና የፎረጀሪ ሥራው የሚታወቅ ሰው ሲሆን ወደ ዳላስም ከመጣ በኋላ በቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን ውስጥ እራሱን ወላጅ ኮሚቴ በማለት ከሚጠራው ማፊያ ቡድን ጋር በመቀላቀል የተለመደ ሥራውን ቀጥሏል፡፡

በቅርቡም በቤተክርስቲያናችን የአስተዳደር ቦርዱ በፖሊስ ኃይል በመጠቀም በቤተመቅደስና በንጹሐን መእመናን ላይ የፈጸመውን ወንጀል በፈጠራ ወሬ ያቀነባበረው አቶ ሃገሬ እንደሆነ እራሱ በፍርድ ቤት በሠጠው የሐሰት ምስክርነት አረጋግጧል፡፡ይኸውም ‹ማኅበረ ቅዱሳን ከፎቅ ላይ ሆነው መብራት አጥፈተው ጫማቸውን ወደመቅደሱና ወደ ካህናቱ ለመውርወርና ለመረበሽ ሲነጋገሩ ሰምቻለሁ› በማለት የተለመደ ፎርጀሪ ወሬውን ለቦርድ በመስበቁ እንዲህ ዓይነቱ ጥፋት ሊደርስ እንደቻለ የቦርድ አባሉ አቶ አበራ ፊጣም በሕግ ፊት መስክረዋል፡፡

አቶ ሃገሬ ይህንኑ ጉዳይ በተመለከተ በካሴት የተቀዳ መረጃ ስላለኝ ለማቀነባበርና በእንግሊዘኛ ተርጉሞ ለማቅረብ የእናንተን እርዳታ እፈልጋለሁ በማለት አንዳንድ ከምንም ነገር ውስጥ የሌሉትን ንጹሐን ሰዎችን በነገር ለማነካካትና ችግር ውስጥ ለመክተት እየሠራ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡
ስለዚህ የአስተዳደር ቦርድ አባላቱን በጥፋታቸው እንዲጠየቁና በአስተዳደር ብልሹነት እያደረሱ ያለውን በደል በሕግ ለማስቆም በፍርድ ቤት እየተሟገታችሁ ያላችሁ ከሳሾች ሁሉ የአስተዳደር ቦርዱ መረጃ አለኝ ብሎ የሚያቀርባቸውን ዶክመንቶች ሁሉ ( Electronically Filter ) እንዲደረጉና ትክክለኛ መረጃነታቸው እንዲረጋገጥ ክቡር ፍርድ ቤቱን በጠየቅ እንድታጣሩ ሰላም ተዋሕዶ ካላት መረጃ በመነሳት ታሳስባለች፡፡

አቶ ሀገሬ ከአስተዳደር ቦርዱ ጋር በመረጃ ቅንብር ዙሪያ ሥራ የጀመረ ስለሆነ በውሸትና በተጭበረበረ አሠራር የተካነው የአስተዳደር ቦርድም ሰውየውን በጸጋ ተቀብሎ በምስክርነት ደረጃ በሕግ ፊት ያቆመው መሆኑ በሥራ ያላቸውን ግንኙነት ይፋ የሚያደርግ ነው፡፡ 

አቶ ሀገሬ ይህንን እኩይ ተግባር እንደ ዕለት አንጀራ ማግኛ አንዱ መንገድ አድርጎ የያዘው ስለሆነ ከእጁ የማይለይ የፎቶና የቪዲዮ ካሜራ ይዞ የሚዞር ነው፡፡

ስለዚህ ምእመናን ሁላችሁ የአቶ ሀገሬን ማነንት በመረዳት ፕሮቴስታንት እንጂ የቤተክርስቲያናችን ልጅ አለመሆኑንም በሚገባ ተገንዝባችሁ፤ በቤተክርስቲያንም ሆነ በማናቸውም ጉዳዮች ላይ ከእግዚአብሔር ሰላምታ ያለፈ ምንም ዓይነት ግንኙነት ከእርሱ ጋር እንዳይኖራችሁ በጥብቅ እናሳስባለን፡፡


2 comments:

  1. Why do you know so much about this person. I think you are the one who needs a real job instead of learning someone else life. GET A LIFE!!!!!

    ReplyDelete
  2. ስለ ሀገሬ የቀረበው መረጃ ትክከለኛና የሚረካ ነው፡፡በእኔም አዕምሮ የነበረ ጉዳይ በመሆኑ የሰላም ተዋሕዶ አዘጋጆችን በቅድሚያ አመሰግናለሁ፡፡ ከእንዲህ አይነቱ መናፍቅና አጭበርባሪ ጋር ሽርክና የጀመረ ቦርድ የቤተ ክርስቲያናችን ጠላትና አፍራሽ ነውና መወግድ አለበት ፡፡ ለዚህ የሕዝቡ ተሳትፎ ወሣኝ ነውና ሁላችንም በአንድነት እንነሣ፡፡

    ReplyDelete

አስተያየት