Friday, September 23, 2011

ውጥረት በዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን !  

በአባ ወልደ ትንሣኤ ለሦስት ወራት ወደ ዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን መምጣት ምክንያት በርካታ ምዕመናን ያደረባቸው ስጋት ቀደም ሲል በሰላም ተዋሕዶ ብሎግ እንደ ተገለጸው ለስደተኛው ሲኖዶስ መንገድ ለመጥረግና ቤተ ክርስቲያኗን ለማስረከብ ተልእኮ እንደሚመጡ መዕምናኑ በትክክል በመረዳታቸው ነው። ቦርዱ በአውደ ምሕረቱ ላይ እየወጣ ይህንን ያለሕዝቡ ፈቃድ አላደርገውም እያለ እየዋሽ ውስጥ ውስጡን ግን ከዲያቆን አንዶዓለም ጋር በመሆን በስውር ጉዞ መጀመሩ፤ ሕዝቡን እንደ አሻንጉሊ እያታለለና እየተጫወተበት እንደሆነ የሚያሳይ ነው።

በዚሀ ምክንያት ይህን የዲያቆኑንና የአስተዳደር ቦርዱን የተንኮል ሥራ የተረዱ አንዳንድ መዕመናን ከእግዚአብሔር ይልቅ የሚያመልኩት ቦርድን ነው ወደሚባሉት አንድኛው ካህን ቤት በመሔድ ስለ አባ ወልደ ትንሣኤ መምጣት ጉዳይ ያላቸው አቁዋም ምን እንድሆነ እንዲያስረዱአቸው መጠየቃቸው ታውቆአል። ካህኑም ከዚህ ቀደም አባ ወልደ ትንሣኤን ዳላስ ቅዱስ ሚካኤል የሚመጡ ከሆነ እኔ የቤተ ክርስቲያኑን ቁልፍ አስረክቤ እሔዳለሁ እያሉ ሲፎክሩ የነበሩ ሲሆን ካህኑ ልጃቸውም በዚሁ ተመሳሳይ አቅዋም እንደነበረ የሚታወቅ ነው ። ይሁን እንጂ እነዚህ አቁዋም የለሽ አባትና ልጅ ካህናት የአስተዳደር ቦርዱ ባደረሰባቸው የማስፈራሪያ ቃል መሠረት በፍርሃት በ 90 ዲግሪ ተገልብጠው ስለ አባ ወልደ ትንሣኤ ትልቅነት ማስታውቂያ ተናጋሪ መሆናቸው ብዙኃኑን አሳዝኖአል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ የአባ ወደ ዳላስ መምጣት ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እያየለ በመምጣቱ እርሳቸውም እዚህ ቢመጡ ከፍተኛ ተቃውሞ እንድሚጠብቃቸው ለራሳቸው ተድውሎ ሊነግራቸው እንደታቀደ ምንጮች ይጠቁማሉ። በኢመርጀንሲ 911 ደውለው ፓትሮል ፖሊሶችን መጥራት እንጂ ከእንግዲሀ ወዲህ የጋርላንድ ሲቲ ፖሊስ ቢሮ የአስተዳደር ቦርዱን የፖሊስ እርዳታ ጥያቄ እንድማያስትናግድ በጠነከረ ሁኔታ መልስ መስጠቱ ታውቆአል

5 comments:

  1. you guys are crazy what is the fault of aba wold tensae ? come on guys i am memen i am reading fethnegest they preached from it ? what is wrong with him ? you said bezu memenan oppose him by the way most of them eat pork why they blame him you guys like dejeselam you are out of chrstianity . wrong way if he is a sinner pray for him instead of opposing him . He is educated and polite father . come and learn from him

    ReplyDelete
  2. why you lie guys ? you are ksashe like mk i know you are mk

    ReplyDelete
  3. ዲ.አንዷለም በሰላም ነው አባ ወልደተንሳኤ መጥተው ይሄ መከረኛ ህዝብ ሲበጣበጥ ካላየሁ ብሎ የአዞ እንባውን ያነባው ምን ለማለት ነው። የሚያገኘው የተለየ ጥቅም አለ ወይ? የአሜሪካ ቤተክርስትያናት እየዞሩ ችግር ለሚቆሰቁሱ ሰዎች ደረቱን ገልብጦ የሚከራከረው ለምንድንነው? መምህር ከሆነ ለምን ወንጌሉን ብቻ አይሰብክም የተቀጠረበትን ብቻ ለምን አይሰራም? ለቦርድና ላሜሪካ ሲኖዶስ ታይቶ በማይታወቅ ሁኔታ ይሄ ሁሉ መገለባበጥ ለምንድን ነው? ከሁሉም የሚያሳፍረው በቅርቡ ከ 1 ወር ምናምን በፊት ሃገር ቤት አንዳንድ የሱ ብጤ ሆድ አደሮች ቤተክርስቲያናችንን እናድሳለን በማለት ተመሳስለው ገብተው ይረብሹ ስለነበረ ይሄንን በንቃት የሚከታተሉ መላው የአዲስ አበባ ሰንበት ትምህርት ቤቶች በተከታታይ የሚደረገው ቤተክርስቲያንን የማዳከም የመናፍቃን እንቅስቃሴ ከበላይ መመሪያ ወጥቶ ተገቢው እርምጃ እንዲወሰድ ቢጠይቁም ከሌሎቹ አባቶች ድጋፍ ቢያገኙም አቡነ ጳውሎስ ግን ለተሃድሶዎቹ ሽፋን እየሰጡ ስላስቸገሩ ወጣቱ እራሱን በራሱ አደራጅቶ ለቤተክርስቲያኔ ለተዋህዶ ከኔ በላይ ማንም የለም ብሎ በአቋም ተሀድሶዎች ላይ እርምጃ መውሰድ ሲጀምር አዝማሚያውን ያልወደዱት አቡነ ጳውሎስ ወዲያው አንድ መግለጫ ያወጣሉ እኔ ካላወገዝኩ ማንም ሰው ማንንን ተሀድሶ እንዳይል የሚል። ምንም እንኳን ይሄንን ቢሉ የሚመለከታቸው ሁሉ ሌሎች አባቶችም አገልጋዮችም ማዘናጊያ መሆኑን ወጣቱ እንዲሁም ሁሉም አማኝ ቤተክርስቲያኑን ከመናፍቃን መጠበቅ እንዳለበት ሰርገው የገቡ ስለሆነ እስኪወገዙ መጠበቅ እንደማይቻል በስፋት ተቀስቅሶ እነሆ በአሁኑ ሰአት መናፍቃኑ እያፈሩ ነው ያሉት። ታዲያ አንዷለም ሆዬ ይሄንን አቡነ ጳውሎስ ህዝቡን ለማዘናጋት ኦርቶዶክሳውያንን በቀን ጅቦች ለማስበላት የተናገሩትን ቃል ጠቅሶ ልክ በሲኖዶስ በአባቶች ጉባኤ የተወሰነ አስመስሎ ማንንም ተሀድሶ አትበሉ ተብሏል ብሎ ሊያዘናጋን ይሞክራል። በመጀመሪያ ደረጃ አቡነ ጳውሎስን ሳይቀበል እርሱ የሚቀበለው ስደተኞቹን ሆኖ ሳለ የሀገር ቤቱን ሲኖዶስና የአቡነ ጳውሎስን ቃል መጠቀም ምን አይነት አጭበርባሪነት ነው? ይሄ ልጅ ወደ ልቡ እንዳይመለስ የዘጋበት ምንድን ነው የተለየ ጥቅም / ገንዘብ፣ ስልጣን፣ ወረቀት/ ምን? ወይስ ሎስ አንጀለስ አለች ከምትባል ጓደናው ጫና? ልብ ይስጥህ አቦ።

    ReplyDelete
  4. selam tawehido( betbach taliban) you do not need the two fathers become agree each other ? dn andulam what ever he work for geen card , or benefit or other he did good job . Go head memhir andualem WE ARE WITH YOU priests, deacons, and believers the two synods problem is only authority, i know the problem ,it , so you guys like devil you are working to become obstacle. mk in adis abeba and small mk and you in U.S.A. so come down guys come and learn on demera st. macheal church

    ReplyDelete
  5. ዲያቆን አንዱአለም የዳላስ ቅዱስ ሚካኢል ቢተክርስቲያን የልጆች አስተማሪ ስለምን የምትናገረወንና የምትሰራወን አታውቕም ? እኛ መሓይሞቹ እኮ ነን ይሀንን ቢተክርስቲያን የመስረትነውና አቁዋቁመን እየተጠቀምንበት አሁን ካለበት ደረጃ ያደረስነው ባደረግነውና በሰራነው መመስገን ሲገባን በቢተከረስቲያኑ መድረክ ላይ ያልሆነውን እውነት አስመስለሀ በተናገርከውና በመስደባችን ልባችን አዝኖብህ መሂዳችንን እንድታውቀው።ለተናገርከው ሁሉ እግዚአብሒር ይቅር ይበልህ ለወደፈቱም ከመናገርሀ በፈት አሰበህ ብትናገር መልካም ነው።

    ReplyDelete

አስተያየት