Friday, February 4, 2011

የፈረንጅ አበሻም አለ ለካ !

ሁሉም ሳይሆኑ ጥቂት የማይባሉ ኢትዮጵያውያን አበሾች ወደ ውጪው አለም ሲወጡ ባህርያቸውን አለባበሳቸውን፤ ባሕላቸውን ሃማኖታቸውን ይለውጣሉ፡፡ ስልጣኔው የራስ የሆነውን ነገር ሁሉ መተው ሰለሚመስላቸው ከተፈጥሮ ቀለማቸው በስተቀር ሁለመናቸውን ይለውጣሉ፡፡ ኢትዮጲያዊ የሚያሰኘውን ነገር ሁሉ ከውስጣቸው በማጥፋት አስኪገርም ድረስ ማንንታቸውን ያጣሉ ፡፡ደሞ ከአበሻ ጋር ፤ የአበሻን ፊቱን አያሳየኝ ወዘተ ... የሚሉትን አባባሎች የምሬት ቃላቶቻቸው ያደርጋሉ፡፡ የተወለዱባትንም አገር ኢትዮጵንም እንደ ሌላ ባእድ አገር ማየት ይጀምራሉ፡፡
ሌላው የአበሻ ዘር ደግሞ ባይወለድባትም የእናት አባቴ ፤ ያያት የቅድማያቴ አገር እያለ ስለ ኢትየጵያና ወገኖቹ ብዙ መልካም ነገር ሲናገር፤ ሲጽፍና ሲያወድስ ይሰማል፡፡ የእናት ሆድ ዥንጉርጉር ነውና እናት የተባለች ኢትዮጵያ ሁሉንም አይነት ሰው አፍርታለች ይዛለች፡፡ 
ነጭ ቀለም ያላቸው አንዳንድ ፈረንጆች በአባቶቻቸውንና በእናቶቻቸው ምክንያት ኢትዮጵያ ሲወለዱ ደግሞ ለኢትዮጵያ ያላቸውን ግምትና ስሜት ምን እንደሚመስል ከሜዲያ ያገኘነውን ቁም ነገር ጠቃሚ ትምህርት ይሰጣል ብለን ስለገመትን አቅርበነዋልና ከታች ያለውን ሊንክ በመጫን እንዲያደምጡ እንጋብዛለን፡

http://www.dw-world.de/popups/popup_single_mediaplayer/0,,14815728_type_audio_struct_12103_contentId_6427031,00.html

No comments:

Post a Comment

አስተያየት