Saturday, August 21, 2010

የሚያኖረን ቸርነቱ ነው !
የእግዚአብሔር ቸርነትና ጸጋ ሃብታሙንም ደሃውንም ፤ ጤነኛውንም ታማሚውንም ፤የሚደስት የሚያዝነውን ወዘተ... ሁሉንም በየደረጃው ያኖረዋል፡፡ ለምሳሌ በሰው ዘንድ ማጣት ችግር በሆንም ፤ በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሰውን በምቾት ምክንያት እግዚአብሔርን እንዳያጣ መጠበቂያ መንገድ ነው፡፡ ሕመም በሰው ዘንድ ስቃይ ቢሆንም በእግዚአብሔር ዘንድ ግን ሰውን ወደ እርሱ ማቅረቢያ ሌለኛው መንገድ ነው፡፡ በዚህ መልኩ ሁሉንም በእኛ የምናየውና ጉዳት የሚመስለን ነገር ሁሉ በእግዚአብሔር ዘንድ በጎና መልካም የሆነ ምክንያት አለውና ነገር ሁሉ ለበጎ መሆኑን አንዘንጋ ፡፡ የሚያኖርን የእግዚአብሔር ቸርነትና ጸጋ እንጂ ገንዘባቸን ወይም ጥበብና እውቀታችን ብቻ እንደሆነ አድርገን እንዳናስብ እንጠንቀቅ፡፡

No comments:

Post a Comment

አስተያየት