ሰላም ተዋሕዶ - ትምህርታዊ የሆኑ የተለያዩ መንፈሳዊ ጽሑፎችን ፤ ዘገባዎችን ፤ በሕብረተሰባችንና በሌላው ዓለም ሕዝብ ባህልና ሕይወት ውስጥ የሚመላለሱ ወጋወጎችን የምታስነብ አስተማሪ ፤ አዝናኝና ቁም ነገር አዘል ብሎግ ናት፡፡Blogging Since Oct 2009
Wednesday, August 24, 2011
Tuesday, August 23, 2011
Tuesday, August 16, 2011
የዳላሱ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን በዲያቆን አንዱአለም መሪነት ወደ ስደተኛው ሲኖዶስ እየሔደ ነው!
‹ከሥጋው ጾመኞች ነን ከመረቁ አውጡልን› በሚል አቋም የኢትዮጵያውንም ሆነ ስደተኛ ሲኖዶስ ነኝ ብሎ አሜሪካ የተቀመጠውን አንቀበልም ፤ ነገር ግን የምንከተለው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን እምነትና ሥርዓት ነው ፤ በማለት የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያን ለበርካታ ዓመታት በዚህ አቋሙ መቆየቱ ይታወቃል፡፡ይሁን እንጂ የቤተ ክርስቲያኑ የቀድሞ አስተዳደር ቦርድ አቋሙን እንደገና በማሻሻል ከጥቂት ዓመታት በፊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሲኖዶስ አይሰደድም፤ሲኖዶስና መንበሩ ያለው አዲስ አበባ ኢትዮጵያ ነው፡፡ሕጋዊው ፓትርያርክም አባ ጳውሎስ ናቸው፡፡ የዳላስ ቅዱስ ሚካኤል ቤተ ክርስቲያንም የኢትዮጵያውን ሲኖዶስ ሕጋዊነቱን ያምናል፤ ይቀበላል ፡፡ ነገር ግን አባ ጳውሎስ ከቤተ ክርስቲያኒቱ ይልቅ በማይመለከታቸውና ሃይማኖቱ በማይፈቅድላቸው ሁኔታ የገዢው ፓርቲ ፖለቲካዊ ተግባር ወኪልና አስፈጻሚ ሆነው እያገለገሉ በመሆናቸው አስተዳደራቸውን አንቀበልም ፤ በማለት የቆየ አስተዳደር ነበር፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)
