Wednesday, April 28, 2010

<ልጆቹዋን ከቅጽሯ የሚያባርሩ ጨካኞች ያሏት ቤተ ክርስቲያን ሊለቀስላት ይገባል።›

የአስተዳደር ቦርድ መልአከ ሣህል አወቀን ከሥራ ካሰናበተበት ሰዓትና ደቂቃ ጀምሮ ባደረበት የፍርሃት መንፈስ ባልተለመደ ሁኔታና ከወትሮው በተለየ መልኩ በርካታ የፖሊስ ሠራዊትን ከሌሊቱ 3 ጀምሮ በቤተክርስቲያኒቱ ግቢ ውስጥ እንዲሠማሩ ማድረጉ ብዙውን አማኝ ክርስቲያን አሳዝኗል፡፡

Saturday, April 24, 2010

አምባ ገነኑ ቦርድ መልአከ ሣህል አወቀን ከሥራ አሰናበተ !

ትናንት ቅዳሜ ማምሻውን ለስብሰባ ይፈለጋሉ ተብለው በስልክ ተጠርተው ቦርድ ጽ/ቤት ተጠርተው የቀረቡት መልአከ ሣህል በሚያስተምሩት እውነተኛ የወንጌል ትምህርት ምክንያት እንደ ክርስቶስ በሐሰት ተወንጅለው አስተዳደርን በማያውቅ አምባገነን ቦርድ የስንብት ደብዳቤ ተነቦላቸው ሁለተኛ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን እንዳይደርሱ በሴት ፖሊስ ተገደው በመፈረም የስንብት ደብዳቤውን ተረክበው መውጣታቸውን ለማውቅ ተችሏል፡፡

Monday, April 19, 2010

የሂሳብ መርማሪና አጣሪ ኮሚቴ የሥራውን ውጤት አቀረበ !

ሰላም ተዋህዶ ቅዳሜ April 17 2010 በተደረገው ጠቅላላ የአባላት ስብሰባ ላይ ያልተካፈለች ብትሆንም ስብሰባውን የተካፈሉ አንዳንድ ሰዎችን በማነጋገር ያገኘችውን ዘገባ በአጭሩ እንደሚከተለው ዘግባዋለች፡፡