በኤፕሪል 25 2010 የዳላስ ደብረ ምሕረት ቅዱስ ሚካኤል አስተዳደር ቦርድ መልአከ ሣህል አወቀን በውድቅት ሌሊት በፖሊስ አስገድዶ በማስፍረም በክህነት ከሚያገለግሉበት የሥራ ገበታቸው ላይ እዲሰናበቱ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ይህንኑ የግፍ አሠራር በመመልከት ቀሲስ መስፍንም ሕዝቡን በዓውደ ምህረት ተሰናብተው በገዛ ፈቃዳቸው ሥራቸውን በመልቀቅ መውጣታቸውም ይታቃል፡፡ ይህንኑ ተከትሎ በተፈጠረ ውዝግብ የአስተዳደር ቦርዱ የቀጠራቸው ኬጂ 9 ቦምብ ፈታሽ ፖሊሶች ወደ ቤተ መቅደሱ በድፍረት ከነጫማቸው በመግባት ምእመናን ከጸሎት ገበታ ላይ በኃይል በመጎተት ደብድበዋል፤ በካቴና ብረትም ጠፍረው በማሰርም አሰቃይተዋል፡፡ ይህም በቴሌቪዥን የታየ ፤ ዓለምን ያስደነቀና ያስቆጣ አስገራሚ ክስተት ብዙዎችን ከቤተክርስቲያኒቱ አሽሽቷል፤አንዳንዶቹንም ሃይሞኖታቸውን እንዲቀይሩ አድርጓል፤ በርካታ የቤተክርስቲኒቱ ምእመናንም በመተባበር ድርጊቱንና አምባገነናዊውን የቦርድ አስተዳደርን በሕግ በመቃወም ጉዳዩን ፍርድ ቤት እንዲመለከተው አድርገዋል፡፡
ሰላም ተዋሕዶ - ትምህርታዊ የሆኑ የተለያዩ መንፈሳዊ ጽሑፎችን ፤ ዘገባዎችን ፤ በሕብረተሰባችንና በሌላው ዓለም ሕዝብ ባህልና ሕይወት ውስጥ የሚመላለሱ ወጋወጎችን የምታስነብ አስተማሪ ፤ አዝናኝና ቁም ነገር አዘል ብሎግ ናት፡፡Blogging Since Oct 2009
Monday, January 31, 2011
Friday, December 3, 2010
አሜሪካኖች ባል ለሚስቱ ምን ያድርግ ይላሉ?
ከሰላዩ ብእር የቀጠለ
ክፍል አራት
ለባለቤቴ እጅግ ጥሩ ባል መሆን እንዳለብኝ ገና ድሮ በወጣትነት ዘመኔ ሳላገባ በፊት አስብ ነበር ፡፡ከዚሁ ጋር በተገናኘ ሀሳብ ብዙ መጻሕፍትን እንብቤአለሁ፡፡ ካነበብኩዋቸው መጻሕፍት ብዙ ዕውቀትና ምክርንም አግንቻለሁ፡፡ ለዚህ ነው ባለቤቴን በተቻለኝ ሁሉ ለማስደሰትና ለመንከባከብ ጥረት ያደረኩት ፡፡ ከባለቤቴ ጋር የነበረንን የሆቴል ቤት ቆይታ ትርኢት ከማጠቃለሌ በፊት ምናልባት አንባቢያን ትምህርት ታገኙበት ይሆናል በማለት አንድ መጽሔት ሳነብ ካገኘሁት ላካፍላችሁ ብዬ ይህንን የእንጊሊዘኛ ጽሑፍ ጋብዤአለሁና አንብቡት ፡፡የተዘረዘረውን ሁሉ ለመፈጸም ቢከብድም ጽሑፉ በትዳር ሕይወት ውስጥ ከሚስት ጋር ሰላማዊ ኑሮን ለመምራት ባል ማድረግ ያለበትንና ሚስት የምትፈልገውን ነገር ሁሉ የሚዘረዝር ነውና አንብባችሁ የራሳችሁን ግንዛቤ ውሰዱ ፡፡
Friday, November 26, 2010
ረዳት ካሜራ
ክፍል ሦስት
እኔም በበኩሌ የባለቤቴ ጠባይ ባልተጠበቀ ሁኔታ መለወጥና በትዳራችን መካከል የነበረው ጣዕም ያለው ፍቅር እየቀዘቀዘ መምጣት እጅግ በጣም አሳስቦኝ ነበር ፡፡ እስከ ሕይወቴ ፍጻሜ ድረስ ከእርሷ ጋር ለመኖር ወስኜና ወድጃት ያገባኋት የትዳር ጓደኛዬን ከምንም በላይ እወዳታለሁ፡፡እርሷ ስሜታዊ ሆና በየምክንያቱ ብትበሳጭም ብስጭቷን የሚያበርድ እንጂ ንዴቷን የሚጨምር ሥራ ሠራሁ የምለው በእኔ በኩል አንዳች ነገር የለም፡፡እሷን የሚያስቀይም መጭፎ ነገር ማደረጌም ጨርሶ ትዝ አይለኝም፡፡ ይሁን እንጂ ለምታሳየኝ አክብሮት ለሌለው ሥነ ምግባሯ ቂም ይዤ ወይም እርሷን በክፉ ለመበቀል በጭራሽ አልሜም አስቤ አላውቅም፡፡የእኔ የሁሉ ጊዜ ምኞት እርሷ በአእምሮዋ ታድሳና ተለውጣ ማየት ነው፡፡ ወዲያው መልሳ ብትረሳውም ከእርሷ ያየሁትና የምወድላት መልካም ነገር ቢኖር ካጠፋች በኋላ የምታደርገው ጸጸት ነው፡፡ ያ እንዳልሰለቻትና እንዳልጠላት አድርጎኛል፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)

